23 January 2019

ኢትዮጵያ ደርሶ መልስ - ታሪካዊ ጉዞ!



በሀገራችን ኢትዮጵያ የተከሰተውን ለውጥ ተከትሎ ብዙሃን በስደት ዓለም ያሉ ወገኖች ወደ ሀገር ቤት የመመለስና ከወገን የመገናኘት እድል እንዳጋጠማቸው ሁሉ እኔም ከብዙ አመታት የስደት ቆይታ በኋላ ወደ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ ከነመላ ቤተሰቤ ለመሄድ ችዬ ነበር:: በሀገር ቤት ያለውን ለውጥ በቅርበት የምከታተል ቢሆንም በተግባር ያየሁት ለውጥ ግን ከጠበኩት በላይ ነው:: አዎ እውነተኛ ለውጥ አለ:: እሰይ በርቱ ከማለት በተጨማሪ ለውጡ ዘላቂ እንዲሆን በተግባር ማገዝ የውዴታ ግዴታ ነው::

ታህሳስ 13 ቀን 2011 (ዲሴምበር 22 )

At the Office of the Mayor of Addis Ababa
ይህ ቀን አዲስ አበባ የደረስኩበት ቀን ሲሆን የመጀመሪያውን መልካም ስራ ያየሁት ቦሌ አለም አቀፍ ኤርፖርት ነው:: የመግቢያ ቪዛ ላይ የሚሰሩት የኢሚግሬሽን ሰራተኞች ቅንነት፣ ፍጥነትና ቅልጥፍና የመጀመሪያው የመልካም ስራ መገለጫ ሆኖ አግኝቸዋለሁ:: 30 ደቂቃ ባነሰ ጊዜ ውስጥ ትህትና የተሞላበት መስተንግዶ ማግኘት እጅግ የሚያስመሰግን ነው:: ይህ ቦታ ሀገራችን ሲደረስ የመጀመሪያው ቦታ ስለሆነ የሰራተኞቹ ብቃትና ቀናነት ብዙ ዋጋ አለው:: በርቱ ሊባሉ ይገባል::

አዲስ አበባ የደረስኩት በምሽት ቢሆንም አዲስ ሞቅ ደመቅ እንዳለችና ከነ ግርግሯ ነበረች። ወደ ማረፊያዬ ጉዞ እያደረግኩኝ በነበረበት ሰዓት የነበረውን የመኪና ብዛትና የሚሯሯጡ ወጣቶች ስመለከት ብዙ ማሰቤ አልቀረም። ለምን ይሆን እነዚህ ወጣቶች በዚህ ምሽት የሚሯሯጡት ማለቴም አልቀረም። እነዚህ ወጣቶች አዲስ አበባ በውስጧ ብዙ የህይወት ገፅታዎች እንዳካተተች አመላካች ከመሆናቸው በተጨማሪ ብዙ መሰራት ያለባቸው ሥራዎች እንዳሉ ያሳየናል። የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ ይህንን አሳሳቢ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማሰገባት አፋጣኝ መፍትሄ ለመስጠት የነደፉት ፕሮጀክት ያለ መሆኑን በከንቲባው ቢሮ በተገኘሁብት ጊዜ የተረዳሁ ሲሆን ፕሮጀክቱ ውጤታማ እንዲሆንና በጎዳና ላይ ያሉትን ዜጎች መልሶ ለማቛቛም የሁሉም ሀገር ወዳድ ዜጋ ርብርቦሽን ይጠይቃል:: ተግባራዊ እገዛ ማድረግ ሀገሩና ወገኑን ከሚወድ ዜጋ የሚጠበቅ ነው።

With Selamawit Dawit, Director General
 of  Ethiopian Diaspora Agency
በአዲስ አበባ ቆይታዬ ባየሁት የህዝብ ተስፋ ሙሉነትና የነፃነት መንፈስ በውስጤ ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅ ያደረገኝ ሲሆን ለስራ በሄድኩባቸው እንደ ኢሚግሬሽን፣ ቴሌ፣ የውጭ ጉዳይ /ር፣ ዲያስፖራ ኤጀንሲና የአዲስ አበባ መስተዳድር ያየሁት የስራ ተነሳሽነትና የተጠያቂነት ስሜት በጣም ተደስቻለሁ::

በአዲስ አበባ ብዙ መልካም ነገሮችን ለማየት የቻልኩትን ያህል ብዙ አሳሳቢ ነገሮች እንዳሉም ለማስተዋል ችያለሁ:: በከፍተኛ ደረጃ የሚጠቀሰው የስራ አጥነትና የትራንስፖርት ችግር ቢሆንም ብዙ ሊሰራባቸው የሚገባቸው ነገሮች እንዳሉ ግልፅ ነው:: የመብራት በየጊዜው መጥፋት፤ የውሃ በድንገት መሄድ መፍትሄ ሊበጅለት ይገባል:: የብር የመግዛት አቅም መውረድም አሳሳቢ ነው:: ብዙ አሳሳቢና ሊሰራበት የሚገባ ጉዳይ  የመኖሩን ያህል በህዝባችን ውስጥ ያለው ተስፋ በጣም አበረታች ነው:: ተስፋ ለስኬት አስፈላጊ የመሆኑን ያህል፤ ስኬት ደግሞ የተግባራዊ ስራ ውጤት ነው::

ዛሬ ነገ ሳንል ሀገራችንን እንደየአቀማችን በተግባር እናግዝ:: ነጮቹ " Walk the Talk” ይላሉ::

Time to Get Out and Vote – Democracy in Action

  United Kingdom goes to the polls on July 4th.  Since the election was called by British Prime Minister Rishi Sunak, I have had the opportu...