20 October 2018

ዛሬን በጎ ነገር ሰርተን ነገን እንገንባ


መቃወምም ሆነ መደገፍ መብት ነው። በውሸት ዜና ለማትረፍ መሞከር ግን አስነዋሪ ነው።

ባለፉት 6 ወራት ብዙ የሚባሉ ሸጋ ክንዋኔዎች የተከናወኑ ቢሆንም በተጓዳኝም ጥቂት የማይባሉ ፈታኝ አጋጣሚዎችንም አስተውለናል። ሆን ተብሎ የውሸት መረጃ በመልቀቅ በህዝቦች መካከል ጥርጣሬ በመፍጠር ለፖለቲካ ትርፍ መሯሯጥ በተደጋጋሚ ይስተዋላል። ያልሆነው እንደሆነ አድርጎ በማውራት፤ ያልተከሰተውን እንደተከሰተ አድርጎ የውሸት መረጃ በመልቀቅ አለመራጋጋት ለመፍጠር ሲሞከር እናያለን። ብዙ መስራት ሲቻል በመጠላለፍ ጊዜ ማባከኑ ምን ይጠቅማል? ዛሬ በጎ ነገር በመስራት ነገ የተሻለ ቀን እንዲሆን ማድረግ የሚያስችል አቅም አለን። ኢትዮጵያ የብዙሃን ሀገር ነች። በፈሪሃ እግዚአብሄር የምተታወቅ ሀገር። አንተ ትብስ፤ አንቺ ትብሽ የመባባል የቆየ የአብሮነትና የመቻቻል እሴቶች የዳበሩባት ሀገር ናት። አኩሪ የሆነ ታሪክ አላት ሀገር። ይህ ሁሉ ሊያኮራንና ወደፊት የበለጠ ለመስራት እንድንተጋ ሊያደርጉን ይገባል እንጂ  ወደ ኋላ ሊጎትቱን አይገባም።
የጋራ ጠላታችን ድህነት ነው። ይህም ከመልካም አስተዳደር እጦት የመጣ ነው። በስልጣን ላይ ያለው የዶ/ር አቢይ አህመድ መንግስት በሀገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ በሚባል ደረጃ የኢትዮጵያውያንን የልብ ትርታ ማዳመጥ የሚችል ስርዓት እንዲመጣ ደፋ ቀና እያለ ባለበት በዚህ ጊዜ ብንችል በመደገፍ የበኩላችንን ማድረግ አለበለዚያ እንቅፋት በመሆን ጥቁር አሻራ ጥለን ላለማልፍ ጥረት እናድርግ። ነገ በተስፋ የተሞላ ቀን እንዲሆን ዛሬ ተግተን እንስራ። ልጆቻችን፣ የልጅ ልጆቻችን ባጠቃላይ መጪው ትውልድ የወደፊት ህይወቱ አስደሳችና የተቃና እንዲሆን ዛሬን ሳናሰልስ በበጎ ነገር እናሳልፈው። 

ዛሬን በጎ ነገር ሰርተን ነገን እንገንባ።


30 September 2018

Stand with Dr. Abiy and win together


The past few months have been full of ups and downs for fellow Ethiopians. We have been full of hope and optimism following the rise into power of Dr. Abiy and his team. Lots of promising achievements in a short period of time. The release of political opponents and critics of the government was a big step forward. Engagement with stakeholders around the country and the world was among the commendable acts of the new Prime Minister. Restoration of peace between Ethiopia and Eritrea was among the major achievements. The return of exiled opponents, activists and leaders was a remarkable achievement. The work to restore freedom of expression and media is also to be applauded. Hence lots to celebrate and remain hopeful. 

Dr. Abiy’s government has not been without challenges. The killing of Engineer Simegnew; the killings and displacements of fellow Ethiopians in different parts of the country is heart-breaking and worrisome. Ethnic based conflicts and tensions remain the major challenge for Dr. Abiy’s government. The incarnation of fellow Ethiopians from Addis and other parts of the country was among the setbacks. Hence despite a very promising start, there have been challenges that need addressing. One thing for sure Ethiopia will not be the same again. The change engineered by Dr. Abiy and team needs to go on and we should give it our 100% support. It is now or never. For sure, it should be now. 

We don’t need to be political giants to influence change. All it needs is our goodwill and concern for Ethiopia that is for all and do our bits. We will encounter challenges through the process, but we need to stick to our ideals, principles and the bigger picture that is Ethiopia for Ethiopians. 

Hence my call is simple.

1.    Give your support to Dr. Abiy and team as they go through challenging time. Don’t expect them to do everything themselves. Rather tell them what you are doing to make the change they are leading a success and long lasting.
2.    Be cautious of allegations and counter allegations - We are in the 21st century where ideas are judged based on their merits. Let us debate on the ideas and come to a consensus.
3.    Avoid triumphalism or defence mechanism - no single individual, activist or party is a winner through the change making progress. We are all winners; and if we lose, we lose together. As a country we cannot afford to lose! 
4.    Character assassination doesn’t help - it rather adds fuel to the fire. It is not bad to challenge individuals or groups, but the challenge should be geared towards their ideas and opinions. We need to back ourselves with facts, realities and logic
5.    Working for peace and reconciliation - this is for all of us to do. Yes, we need Peace and Reconciliation Commission organised by the senior leadership of the country. But this doesn’t stop us from working for peace, reconciliation and tolerance locally. After all it is customary for Ethiopian elders to do this. That is the Ethiopia I know.
6.    Civic and political engagement- whether we like it or not politics affects our lives. Hence, we need to be political, not necessarily politicians. We need to be politically active and help the change. We should at the same time strengthen our civic institutions such as ‘Equb, Edir, Mahber, etc’. They are our foundations for civic and political engagements.
7.    Responsible journalism and social media usage – In this day of social media and public journalism, we need to be very cautious and work more on what unites us than divides us. Our media needs to be independent, robust, investigative and above all that can engage most if not all. This doesn’t mean some media outlets will not be mouthpieces of individuals, groups or political parties. Rather we should work to have strong, professional, ethical and independent media.

All the above could happen if we continue to give our unwavering support to Dr. Abiy and his team. Together we can make tomorrow a better day.


19 September 2018

አምባገነንነትን በጀብደኝነት ከተካን ወደ አምባገነንነት መመለሳችን አይቀርም


ጥቂት 'የፖለቲካ አክቲቪስቶች' በኢትዮጵያ የተከሰተውን ለውጥ በግላቸው ያመጡት እንደሆነ ደጋግመው ሲያወሩ ይሰማል:: ግልፅ መሆን ያለበት የተገኘው ውጤት የመላው ኢትዮጵያውያን የዘመናት የትግል ውጤት መሆኑን ነው:: ግለሰቦች ተነስተው ለውጡን እኔ ነኝ ያመጣሁት፤ እንደፈለገኝ መሆን እችላለሁ ሲሉ ዝም ብለን ልናያቸው አይገባም:: ዝምታ ባበዛን ቁጥር እነዚህ ግለሰቦች በጀብደኝነት ናላቸው ይዞራል:: በጀብደኝነት የሚሰራ ስራ ደግሞ ሚዛናዊነትን ሊያጣ ይችላል:: ችኩልነትም ይኖረዋል:: ለዚህም ነው ከአሁኑ ጥንቃቄ ማድረግ የሚገባን:: ሳይቃጠል በቅጠል ይባላል::

ከመንግሥት ከተፎካካሪ ፓርቲዎችና ከሚዲያው ምን ይጠበቃል?

1. ለሰላምና እርቅ በጋራ መሥራት - በሀገራችን ለዘመናት ሲዘራ የኖረው ዘርን መሰረት ያደረገ ቅስቀሳ በህዝቦች መካከል አለመተማመን መፍጠሩ አልቀረም:: ይህ አለመተማመን በለውጡ ላይ ተፅዕኖ አለው:: ተፅዕኖውም በግልፅ እየታየ ነው:: በህዝቦች መካከል ግልፅ የሆነ ውይይት ማድረግ አስፈላጊ ነው:: ችግሩ ምንድን ነው? የመፍትኄ ሃሳቡስ ብሎ መጠየቅና ጥልቅ የሆነ ውይይት ማድረግ ይገባል:: ችግሮችን አድበስብሰን ማለፍ የለብንም:: ችግሮቻችንን በውይይት የመፍታት ባህል ማዳበረ አለብን:: በሃሳብ አለመግባባት ወይም አለመስማማት ወደ ፀብ ሊወስደን አይገባም:: ላለመስማማት ተስማምተን አብረን መጓዝ እንችላለን (We need to agree to disagree):: ይህ ትልቅ የአመራር ብቃት ይጠይቃል::

2. ለተቋማት ግንባታ ቅድሚያ መስጠት - የተጀመረው ለውጥ መቀጠል የሚችለውና ዘላቂ የሚሆነው ለዲሞክራሲ ግንባታ አስፈላጊ የሆኑ ተቋማት በጊዜው ሲገነቡ ነው:: ከግለሰብም ሆነ ከፖለቲካ ፓርቲ ተፅዕኖ ነፃ የሆኑ ተቋማት ከገነባን ብቻ ነው በኢትዮጵያችን ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ማስፈን የምንችለው:: እነዚህ ተቋማት ዋስትናዎቻችን ናቸው:: ስለዚህም ቅድሚያ ልንሰጣቸው ይገባል::

3. የሚዲያ ነፃነትና ተጠያቂነት - በሀገራችን ያሉት የሚዲያ ተቋማት ነፃነት ሊኖራቸው የሚገባውን ያህል ተጠያቂነት እንዳለባቸውም መዘንጋት የለባቸውም:: ጀብደኝነትንና የጥላቻ ወሬዎችን በተደጋጋሚ ማስተናገድ ዋጋ ያስከፍላል:: ለሀገርና የህዝብ ደህንነት ስጋት የሆኑ መልዕክቶች ከመተላለፋቸው በፊት ጥንቃቄ ማድረግ አስፈላጊ ነው:: የተጠያቂነት ባህልን ማዳበር ይገባል::

4. የሥራ ፈጠራና የኢኮኖሚ ግንባታ - በሀገራችን የሥራ አጥነት በስፋት መኖሩን መዘንጋት የለብንም:: ብዙ ሥራ መስራት የሚችሉ ነገር ግን የሥራ እድሉን ያላገኙ ወጣቶች እንዳሉ የታወቀ ሲሆን ይህንን እምቅ ኃይል ለሀገር ግንባታ ለመጠቀም ሁኔታዎችን ማመቻቸት አለብን:: ከሀገራችን ሀብቶች አንዱ የሰው ኃይላችን ነው:: የሥራ ፈጣሪነትን በማበረታታት ይህን እምቅ ኃይል ለሀገር ግንባታ ልናውለው ይገባል:: ይህ ኃይል የሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ዋልታና ደጀን መሆን ይችላል:: ኢንቬስትመንት ወደ ሀገራችን እንዲገባና ህዝባችንም ተጠቃሚ እንዲሆን መንግስትም ሆነ የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ ሳያሰልሱ መስራት አለባቸው:: በተጓዳኝም ሲቪል ሰርቪሱ ከተንዛዛ አሰራርና ሙሰኝነት ነፃ መሆን አለበት:: ለዚህም መሳካት ሁሉም የበኩሉን ማድረግ ይጠበቅበታል::

ሀገራችንን የማገዝና የማሳደግ ግዴታው የሁለችንም ነው:: ዛሬ ነገ ሳንል ሀገር ግንባታ ላይ ማተኮር አለብን::

7 September 2018

ኢትዮጵያዬ የኔ ናፍቆት




ኢትዮጵያዬ የኔ ናፍቆት
ትውስ አልሽኝ እናት አለም

አውዳመቱ፣ ግርግሩ፣ 
ድርድሩ፣ ፉክክሩ
አንተ ትብስ 
አንቺ ትብሽ
ስንባባል የኖርንበት
እረ ስንቱ ኢትዮጵያዬ
ስንቱን ላንሳ፤ ስንቱን ጥዬ 
ከትዝታው፣ ከትውስታው

ልንገርሽ እናት አለም
ላጫውትሽ ኢትዮጵያዬ
በውስጤ የኖረውን

በጥቂቱ ልንገርሽ
ከታሪኬ ላካፍልሽ
ኢትዮጵያዬ ላውጋሽ
ትዝታዬን ላጫውትሽ

በአየር ክልልሽ ያለፍኩት 
በሰማይሽ ያቋረጥኩት 
አልረሳውም ኢትዮጵያዬ 
የተሰማኝን ስሜት
የነዘረኝን ንዝረት

የኢትዮጵያ አየር ክልል 
ውስጥ ነህ ቢለኝ ካርታው

ኢትዮጵያን እያለፍናት ነው 
ቢለኝ ያልገባው ጎረቤቴ
በመፅሃፍ ተደብቄ
ሥራ የበዛበት ሆኜበት 
እንባ እየተናነቀኝ
አንዲትም ቃል ትንፍሽ ሳልል
አለፍኩሽ እኮ ኢትዮጵያዬ::

ዛሬ ግን ኢትዮጵያዬ
አዎ ዛሬ ግን ሀገሬ 
የተስፋ ስንቄን ሰንቄያለሁ 
ብቅ ብዬም አይሻለሁ

የአቅሜንም ጀባ እላለሁ
ብድርሽንም እከፍላለሁ

ኢትዮጵያዬ እንገናኛለን 
ዳግምም እንተያያለን

ትናንት ኢትዮጵያዊ
ዛሬም ኢትዮጵያዊ
ነገም ኢትዮጵያዊ
ሁሌም ኢትዮጵያዊ
ኩሩው ኢትዮጵያዊ

እመጣና አይሻለሁ
የአቅሜንም ጀባ እላለሁ
ቃሌንም አከብራለሁ::

(ማስታወሻነቱ በስደት ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን)


30 August 2018

Farwell to The Towering figure of Community Organising


 “If you are a player, you make change happen. If you are an observer, you watch it happen.” – Neil Jameson CBE, Executive Director of Citizens UK


I am in a mixed feeling as I write this piece to pay tribute to Neil Jameson, one of the best human beings I have ever met in my life. Sad that he is stepping back from the organising work he has been doing for over 30 years. Sad that relational person, one of the kindest folks you can ever meet will not be around when you go to the office. Sad that the man who is not only the founder, Executive Director of Citizens UK and the most senior community organiser in the country, but also a good friend to all the staff members has decided to step back. Yes, Neil is stepping back, as he wants to call it, as of 1st September 2018.  But I am glad that he will have more time to support the work of our new and young foundation, Sponsor Refugees and the wider Community Sponsorship movement. I will have more of Neil’s time to hear from his bank of stories and get even more inspired.


I met Neil over 10 years ago. Then I was a stranger. Someone stuck in the immigration system.  Waiting and waiting and waiting. Those days were challenging for me in life, but I wasn’t alone. There were a lot of people that were stuck in the system and waiting for decisions from the home office. That was when we had the Strangers into Citizens campaign that was led by the then Citizen Organising Foundation. A campaign that changed the lives of many, but not talked about that much.

I was thus given opportunity to join the National Residential training that took place from 10th – 14th March 2008 at Chigwell Convent in East London. I was invited to the training by Jonathan Cox, who is now Deputy Director of Citizens UK. He was then the Co-ordinator of The Independent Asylum CommissionThat training changed my life for ever. That was a turning point for me. Prior to that training, my campaigns were not that organised.  I was rather a lone wolf who often took time to write about the human rights situation in Ethiopia and on issues related to asylum, immigration and the need for democracy in Africa. A bit disorganised. That was then.

In March 2011, I joined Citizens UK as a Community Organiser. This rewarding job brings me in touch with people from across the world who relentlessly work hard to change the world. I have gone from being a detainee at Harmondsworth detention centre to spending time at Harvard Kennedy School, Harvard University studying Global Change and Leadership. In 2017 Neil encouraged me to put in application for Churchill Fellowship. After lots of contemplation, I decided to go for it. Luckily I made it and became one of the 2018 Churchill Fellows and have since traveled to Canada to do research as a fellow. All this wouldn’t have happened had it not been for Citizens UK, its founder and Executive Director, Neil Jameson. I am so grateful and will remain so.

The community Organising world will be missing Neil enormously. It will be tough not to have the gentle giant of Community Organising around. Tears may not come out of my eyes, but my heart and the hearts of many other colleagues and leaders will weep and cry in silence. Because we will be missing the father of Community Organising in the UK.

Kudos to you Neil. Thank you for all you have done for me and many others and for your dedication and unwavering commitment for social justice. The world is a better place because of people like you.


29 August 2018

ዲያስፖራው ለሀገሩ


በውጭ የምንኖር ኢትዮጵያውያን በአብዛኛው ጊዜ ስለ ሀገር ጉዳይ ከመወያየት ተቆጥበን አናውቅም:: አልፎ አልፎም መከራከራችን አይቀርም:: በሃሳብ ልንለያይም እንችላለን:: በሃሳብ መለያየት ክፋት የለውም። በሃሳብ መለያየታችን ለዲሞክራሲ ግንባታ የበኩላችንን ከማድረግ ሊያግደን አይገባም:: አብረን ከመስራትም ሊያግደን አይገባም::

ዛሬ ነገ ሳንል  ተግባራዊ እንቅስቃሴ በማድረግ በሀገራችን ኢትዮጵያ የተጀመረውን የለውጥ ጉዞ  ማገዝ ኢትዮጵያዊ ኃላፊነታችንና ግዴታችን ነው:: ተግባር ከብዙ ቃል በላይ ይናገራል ይባላልና እራሳችንን በተግባር የምንፈትሽበት ጊዜ ነው:: ሀገራችን ከአምባገነናዊ ሥርዓት ተላቃ በሽግግር ላይ  ያለች እንደመሆኗ መጠን ከምንም ጊዜ በላይ የልጆቿ እገዛ  ያስፈልጋታል።

ዲያስፖራው  ለውጡን በብዙ መልኩ ማገዝ ይቸላል፣ ዋናው ቁርጠኝነት ነው። 

በሀገራችን የተከሰተው ለውጥ ስር ነቀልና ዘላቂ እንዲሆን ከምንም በላይ የተቋማት ግንባታ ያስፈልጋል:: ሲቪክ ማህበራት፤ ነፃ የሚዲያ ተቋማት፤ ከፖለቲካ ፓርቲ ተፅእኖ የተላቀቀ ሲቪል ሰርቪስ እና ሌሎችም ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶች በሙሉ እንዲሟሉ ዲያስፖራው በብዙ መልኩ እገዛ ማድረግ ይችላል። ይህ ተግባራዊ እንዲሆን ሁሉም በሆደ ሰፊነትና ይቅር ባይነት መንፈስ ሊነሳሳና ነገ የተሻለ ቀን እንዲሆን ሊሰራ ይገባል። ትናንት አብረን ስላልሰራን ነገም አብረን መስራት አንችልም የሚል አመለካከት ጊዜው ያለፈበትና ያረጀ ነው። በፖለቲካው ዓለም ዘላለማዊ ወዳጅ ወይም ዘላለማዊ ጠላት የለም ይባላል። ሁሉም በህሊናው ልክ ነው የሚለውን ነገር ለማሳካት ነው የሚሰራው። በዚህ ሂደት ውስጥ ደግሞ ለድርድር የማይቀርቡ ነገሮች እንደሚኖሩት ሁሉ የጋራ የሚያደርጉን ብዙ ነገሮች አሉ። ኢትዮጵያ የሁላችን ነች። ኢትዮጵያ የጋራችን ነች። ከአንድ ቤተሰብ የተፈጠሩ ግለሰቦች በእናታቸው አይደራደሩም። ወፈርችም ቀጠነች፤ አጠርችም ረዘመች፤ ደሃም ሆነች ሀብታም፤ እናት ሁሌም እናት ነች። ኢትዮጵያም ኢትዮጵያ ናት።

ኢትዮጵያውያን ዲያስፖራዎችን አንድ የሚያደርገን ከምንም በላይ ኢትዮጵያዊነት ነው። ሀገራችን በበጎ እንጂ በክፉ ስሟ አንዲነሳ አንፈልግም። ወደድንም ጠላን ሀገራችን ሀገራችን ነች።  የሀገራችን በኢኮኖሚ ወደ ኋላ መቅረት ጠንክረን በህብረት ያለመስራታችን ውጤት ነው። ለዚህም የነበሩት ስርዓቶች ተፅዕኖ ያደረጉብን መሆኑ የማይካድ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ያገኘነውን መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ሀገራችንን ልናግዛትና የበኩላችንን ልናደርግላት ይገባል፣ ይቻላልም። ላለፉት አያሌ አመታት በዓለም ዙሪያ የተበተኑት ኢትዮጵያውያን በየሀገሮቹ ካሉት ኤምባሲዎች ጋር ያላቸው ግንኙነት እጅግ በጣም አናሳ ነበር። በዚህም ምክንያት በዲያስፖራውና በኤምባሲዎች መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ የበዛበትና ብዙ ወደፊት መሄድ የማይችል ነበረ። ይህ የቆየና ስር የሰደደ አመለካከት ከጊዜው ጋር ሊለወጥ ይገባል። መጥፎ ነገሮችን እንደምናወግዝ ሁሉ በጎ ነገሮችን ደግሞ ማወደስና ማበረታታት ይገባል። ኢትዮጵያዊ አብሮ መብላት እንጂ አብሮ መስራት አይችልም የሚለውን የቆየ አባባል ማክሸፍ ይገባል። በልዩነት ላይ ተስማምቶ አብሮ መስራት እንደሚቻል በተግባር በማሳየት የተለወጥን ሰዎች መሆናችንን ማሳየት አለብን። ጊዜው ሲደርስ ዜጎች ከኤምባሲዎቻቸው ጋር መልካም ግንኙነት ፈጥረው ብዙ ለሃገር የሚበጅ ስራ መስራት ይቻላሉ። ያኔ ሁሉም ይሆናል። እስከዚያው ግን ዲያስፖራው በግሉና በተደራጀ መልኩ ብዙ ነገሮችን ማከናወን ይችላል።  

የሚከተሉትን ማከናወን ለሞራል እርካታ ከማገዙም በላይ ሀገራዊ ግዴታን ለመወጣት ይጠቅማል።

1.       የውይይት መድረኮችን፣ ኮንፈራንሶችን፣ ልዩ ልዩ ዐውደ ጥናቶችን በማዘጋጀት ህዝባችን የተገኙትን ለውጦች እውቀቱን፣ ገንዘቡን፣ ጊዜውን በመስጠት በተግባር ማገዝ እንዲችል ማበረታታት።
2.    ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ዜጎች የገንዝብ እገዛ እንዲያደርጉና ገንዘባቸውም ለታቀደለት ዓላማ እንዲውል ንቁ ተሳትፎ ማድረግ።
3.       ዜጎቻችን ወደ ሀገራቸው በመሄድ እወቀታቸውንና ጊዜያቸውን ለወገኖቻቸው እንዲያካፍሉ ማበረታታት።
4.       ዜጎቻችን ከሀገር ቤት የሚያገኙትን እውቀትና ልምድ በሚኖሩበት ሀገር ለሚገኙ ወገኖች ማካፈል የሚችሉበትን መድረክ ማመቻቸት።
5.       ዜጎች የውጭ ትምህርት እድል እንዲያገኙ ጥረት ማድረግ፣ አስፈላጊ ሆኖ ሲግኝ በተደራጀ መልኩ ማገዝ።
6.       ኢንቨስትመንት ወደ ሀገር ቤት እንዲገባ ማበረታታት::
7.       ሀገራችን ከቱሪስቶች ጉብኝት የውጭ ምንዛሬ ልታገኝ የምትችለበትን ሁኔታ መፍጠር
እነዚህንና ሌሎች ተግባራትን በተደራጅ መልኩ በማከናወን ሀገራዊ ግዴታን በመወጣት ከህሊና ወቀሳም መዳን ይቻላል። ከምንም በላይ ግን ለዲሞክራሲያዊ ተቋማት ግንባታ ዲያስፖራው ከፍተኛ እገዛ ማድረግ ይችላል ። ይጠበቅበታልም።

ቸር እንሰንብት።


21 August 2018

ለበሬ ወለደ ዜና ቦታ የለንም


                             

የሶሻል ሚዲያ የውሸት ዜናዎች (Fake News) ሊያሸብሩን አይገባም!

በሀገራችን የተከሰተውን ለውጥ ተከትሎ ብዙ በሬ ወለደ ዜናዎች በሶሻል ሚዲያ ውጤቶች በተለይም በፌስ ቡክና ቲዩብ ( Facebook and You tube) በብዛት ተሰራጭተው እናያለን። እነዚህ የበሬ ወለደ ዜናዎች ብዙሃን ወገኖቻችንን ሊያሳስቱና ሊያስጨንቁ ይችላሉ። ህዝባችን የውሸት ዜናዎችን አጥብቆ መታገል ይገባዋል። ከምንም በፊት ለነዚህ የውሸት ዜናዎች ቦታ ባለመስጠት፤ አስፈላጊ ከሆነም የውሸት ዜናዎቹ በሚለቀቁበት ጊዜ የወሬዎቹን ምንጭ በመጠየቅ ብዙ ጥፋት ሳያስከትሉ ሊያስቆማቸው ይገባል።

የወሸት ዜናዎች በተለያዩ ምክንያቶች ሊፈጠሩ የሚችሉ ሲሆን የተለያየ አላማዎችም አሏቸው።

1. የፖለቲካ ለውጡን ለማወክ የሚደረግ ጥረት፥ በሀገራችን የተከሰተው ለውጥ ደጋፊ እንዳለው ሁሉ ተቃዋሚም አለው። ይህ ደግሞ በለውጥ ሂደት ውስጥ ብዙ ጊዜ የሚከሰት ነው። የፖለቲካና የኢኮኖሚ ጥቅማቸው የሚነካባቸው ግለሰቦችና ድርጅቶች በተቻላቸው መጠን የለውጥ ሂደቱን ከማወክ አይቆጠቡም። ለዚህም የተቻላቸውን ያህል በማድረግ ለወጡ እንዳይሳካና ህዝቡ በለውጡ ላይ ጥርጣሬ እንዲኖረው ለማድረግ ብዙ ጥረት ያደርጋሉ። ለውጡ እንዲቀለበስ ሌት ተቀን ተግተው ከመስራት አይቆጠቡም። እኩይ አላማቸውን ለማሳካት ብዙ ገንዘብ በማውጣት የተቻላቸውን ሁሉ ያደርጋሉ። ይህ የውንብድና ሥራ ብዙም ስለማያስኬድ በዚህ ተልካሻ ተግባር ላይ የሚሳተፉ ግለሰቦችና ድርጅቶች ሌሎች ለውጥ የማደናቀፍ ተግባራት ላይ ከመሳተፍ አይቆጠቡም። ህዝባችን በሀገራችን ለተከሰተው ለውጥ ዘብ በመሆን ለውጡን እንደ ዓይኑ ብሌን ሊጠብቀው ይገባል።

2. የገንዘብ ፍቅር፤ በገንዘብ ፍቅር የተለከፈ ሰው ለገንዘብ ሲል ብዙ አሳፋሪ ተግባራት ሊፈጽም ይችላል። በተለይ ከዩ ቲዩብ (You Tube) ለምትገኝ ጥቃቅን ጥቅማጥቅም ኃላፊነት የጎደላቸውና ምንጭ አልባ የውሸት ዜናዎች ሲለጥፉ እያየን ነው። በእንደዚህ አይነቱ ተልካሻ ተግባራት ላይ የሚሳተፉ ሰዎች ብዙውን ጊዜ የሚያሳስባቸው ምን ያህል ሰው የለጠፉትን ቪዲዮ እንዳየው ማወቅ በቻ ነው። ይህ ተግባር አሳፋሪ ነው። ሊታረምም ይገባል። ህዝባችንም አጥብቆ ሊታገለው ይገባል።

3. 15 ደቂቃ ታዋቂነት መሻት (15 minutes social media fame) የተለያዩ የውሸት ዜናዎችን በተለይ በፌስ ቡክ ላይ በመለጠፍ ለሚያገኙት ላይክ ( like ) ብቻ የሚጨነቁና ያም ታዋቂነት የሚያፈራላቸው የሚመስላቸወ ሰዎች አሉ። ይህ አይነቱ ተግባር በአብዛኛው በፌስ ቡክና ትዊተር ሲከሰት ይስተዋላል። ህዝባችን የዜናዎችን ምንጭ የመጠየቅ ባህል ሊያዳበር ይገባል። ሁሌም ሳናታክት ዜናው እንዴትና ከማን እንደመጣ መጠየቅ አለብን።

4. በየዋህነት የተነገረውን ሁሉ ማሰራጨት፤ ከዘመዴ፣ ከጓደኛዬ፣ ከውስጥ አዋቂ ምንጭ ያገኘሁት ነው በሚል የፈጠራና የውሸት ዜናዎች ሲሰራጩ ይታያል። አልፎ አልፎ የምናያቸው የውሸት ዜናዎች በየዋህነት የሚሰራጩ ናቸው። ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል። በተለይ ከውስጥ አዋቂ ምንጭ እንዳገኘሁት የምትለዋ ሊሰመርባት ይገባል። ግልፅ መሆን ያለበት ሁላችንም የውስጥ አዋቂ ምንጭ ሊኖረን አይችልም። 100 ሚሊዮን ህዝበ ባለባት ሀገር ላይ 100 ሚሊዮን የውስጥ አዋቂ ምንጭ እንደመጥቀስ ነው። ጎበዝ ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው ይሉ የለ አበው። ጠንቀቅ ማለት ይገባል። መጠየቅ፤ ተጨማሪ ምርምር ( research )ማድረግ ይገባል።
ለውጡን የመጠበቅ ኢትዮጵያዊ ግዴታ አለብን። በየጊዜው የሚፈጠሩ የውሸት ዜናዎች ሊያውኩንና ሊያሳስቱን አይገባም። አበከረንም ልንታገላቸውም ይገባል።

ለነ በሬ ወለደ ቦታ ባለመስጠት የለውጥ ጉዟችንን በጋራ እንጓዝ። ኢትዮጵያችንን በህብረትና በዓላማ ፅናት እንጠብቃት።

The Global Refugee Forum – time for meaningful participation of Refugees

  As the Global Refugee Forum takes place between 13 - 15 December 2023 in Switzerland, it is vital that we have meaningful participation of...