14 December 2021

ዲያስፖራው ለሀገሩ ፣ ኢትዮጵያን በጋራ ወደ ከፍታ

 

የዲያስፖራ ኮሚኒቲዉ ወደ ሀገር ቤት በብዛት ለመግባት እየተዘጋጀ ባለበት በአሁኑ ወቅት ብዙ ነገሮችን ማሰብ ተገቢ ነው። ዲያስፖራው ወደ ሀገር ቤት መግባቱ በራ ፖለቲካዊ ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታው ብዙ ነው። ዲያስፖራው ብዙ ማድረግ ይቻላል። ይህ ጊዜ ከምንም ጊዜ በላይ ለሀገራችን ገንዘባችንን ፣ እውቀታችንን ፣ ጉልበታችንን ፣ ልምዳችንን የምንሰጥበትና በጦርነት ለተጎዱ ወገኖች ተግባራዊ ስራ በመስራት ለወገኖቻችን አለኝታ መሆናችንን የምናሳይበት ነው:: በሀገር ቤት ያሉ እንደ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ዲያስፖራ ኤጀንሲ ፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ፣ አደጋና መከላከል ኮሚሽን፣ ትምህርት ሚኒስቴር ፣ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴርና ሌሎች ሲቪክና ልዩ ልዩ ተቋማት በተቀናጀና በተናበበ መልኩ አጋጣሚውን ሊጠቀሙበት ይገባል። ዲያስፖራው በቡድን በመሆነ በተለይ በጦርነቱ በተጎዱ አካባቢዎች እንደ ትምህርት ቤት ግንባታ ፣ የጤና ተቋማት ግንባታና በጣም ወሳኝ በሆኑ የመሰረተ ልማት ስራ ላይ እንዲሰማራ ሁኔታዎች ሊመቻቹለት ይገባል። ዲያስፖራው ለሀገሩ ያለውን ፍቅር በዓለም ዙሪያ አሳይቷል። በተጨማሪው ብዙ አቅም እንዳለውም አሳይቷል። ዋናውና ወሳኙ ጥያቄ ይህንን የዲያስፖራውን እምቅ አቅም ለመጠቅም ዝግጁ ነን ወይ የሚለው ላይ ነው። ለዚህ ተግባራዊነት በተለይ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ከፍተኛ ኃላፊነት አለበት።

ከላይ የተጠቀሱት አስቸኳይና ወቅታዊ ተግባራትን ማከናወን እንዳለ ሆኖ ዘላቂና አሳታፊ እቅዶችን ማዘጋጀትና ለተግባራዊ እንቅስቃሴ መዘጋጀት ኢትዮጵያ በጋራ ወደ ከፍታ ለመውሰድ ጠቀሜታው ብዙ ነው።

በተጨማሪም ዲያስፖራው በግሉና በተደራጀ መልኩ ብዙ ነገሮችን ማከናወን ይችላል።

የሚከተሉትን ማከናወን ለሞራል እርካታ ከማገዙም በላይ ሀገራዊ ግዴታን ለመወጣት ይጠቅማል።

1. የውይይት መድረኮችን፣ ኮንፈራንሶችን፣ ልዩ ልዩ ዐውደ ጥናቶችን በማዘጋጀት ህዝባችን የተገኙትን ለውጦች እውቀቱን፣ ገንዘቡን፣ ጊዜውን በመስጠት በተግባር ማገዝ እንዲችል ማበረታታት።

2. ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ዜጎች የገንዝብ እገዛ እንዲያደርጉና ገንዘባቸውም ለታቀደለት ዓላማ እንዲውል ንቁ ተሳትፎ ማድረግ።

3. ዜጎቻችን ወደ ሀገራቸው በመሄድ እወቀታቸውንና ጊዜያቸውን ለወገኖቻቸው እንዲያካፍሉ ማበረታታት።

4. ዜጎቻችን ከሀገር ቤት የሚያገኙትን እውቀትና ልምድ በሚኖሩበት ሀገር ለሚገኙ ወገኖች ማካፈል የሚችሉበትን መድረክ ማመቻቸት።

5. ዜጎች የውጭ ትምህርት እድል እንዲያገኙ ጥረት ማድረግ፣ አስፈላጊ ሆኖ ሲግኝ በተደራጀ መልኩ ማገዝ።

6. ኢንቨስትመንት ወደ ሀገር ቤት እንዲገባ ማበረታታት።

7. ሀገራችን ከቱሪስቶች ጉብኝት የውጭ ምንዛሬ ልታገኝ የምትችለበትን ሁኔታ መፍጠር ።

8. ዜጎች ህጋዊ በሆኑ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች በመጠቀም ሀገራችን የወጭ ምንዛሪ እንድታገኝ ማድረግ።

እነዚህንና ሌሎች ተግባራትን በተደራጅ መልኩ በማከናወን ሀገራዊ ግዴታን በመወጣት ከህሊና ወቀሳም መዳን ይቻላል። ከምንም በላይ ግን ለዲሞክራሲያዊ ተቋማት ግንባታ ዲያስፖራው ከፍተኛ እገዛ ማድረግ ይችላል ። ይጠበቅበታልም።

8 November 2021

Ganging up on Ethiopia, a proud black nation

 

Many of us strongly feel there is a coordinated attack on our country Ethiopia by the Mainstream media and western political apparatus to portray Ethiopia as if it is full of crises and a no-go-zone. That is not what Ethiopia is. Most of Ethiopia is peaceful. People are living their daily lives without any challenges. It is business as usual in most parts of Ethiopia.

We have to remember that Ethiopia is a country of more than 115 Million people and 1.104 million km² in size. There are more than 90 distinct ethnic groups in Ethiopia. It is also vital to remember that Ethiopia is not only about Tigray, where the current conflict emanated from. Ethiopia is bigger than any region or any ethnic group.

There is indeed a conflict in the North of Ethiopia due to the belligerence act of the Tigray People's Liberation Front (Sanctioned by the Ethiopian Parliament as a terrorist organisation). This organisation has extended its belligerence acts and invaded the Amhara and Afar regions. It has massacred 1000s of innocent civilians. Destroyed livelihoods. Displaced more than a million people. Most of us feel the pain on a daily basis. We still suffer from the trauma of this organisation’s cruelty when it was in power. Many of us in the diaspora left Ethiopia because of this organisation, as it did not tolerate dissenting voices when it was in power. In fact it does not tolerate dissenting voices even today.

Today, Ethiopians feel dismayed; Ethiopians feel frustrated by the false narratives of the Mainstream media which are not representatives of the situations in Ethiopia. And those of us who live in the western world feel very sad to see totally biased reports on Mainstream media outlets including the BBC and The Telegraph. To see intentional misinterpretations and mistranslations of the Prime Minister’s speeches and writings, is even frustrating and disheartening. To see Mainstream media and western political forces ganging up to pressurise a proud black nation is even heart-breaking. And to see this in the era of black lives matter movement is extremely saddening. One would expect to see an honest and ethical translation with accountability when one sees articles on Mainstream media. That is not what has been happening. We have seen photoshoped pictures used by the Mainstream media. We have seen photos of different stories and times used totally for unrelated stories. We have seen those who have no clue at all about Ethiopia being given platforms to speak about Ethiopia – more catholic than the Pope himself? The list is endless.

We just question if there is ever true journalism at all? Most of us have lost our confidence in the Mainstream media and have resorted to citizen journalism using our own means.

The situation in Ethiopia is affecting every Ethiopian for a number of reasons. Those of us in the diaspora see our home country portrayed as a war zone. As if it was a hell on earth. Mainstream Media carrying totally flawed and biased articles. Heart-breaking to see the Mainstream media ganging up on Ethiopia. Very depressing. Hence those who support the law enforcement by the federal government of Ethiopia demand equal treatment of the media.

In the meantime, we use social media to expose the hypocrisy of the Mainstream Media using Social media.


25 October 2021

Coup in the Sudan – what does it mean for Ethiopia?



Late 2018 and early 2019 was monumental for Sudan. The people of Sudan were defiant in their persistent struggles for change. Their struggles to bring change was mostly led by young people and women. We remember the iconic Alaa Salah, whose photo went viral globally. She was just inspirational.

Following the removal of long-time dictator Omar Al Bashir, Ethiopia supported the people of Sudan as they worked on their transition. Ethiopia indeed played a significant role in those days. The people of Sudan had hopes and aspirations. Civil society started to flourish. There were many positive developments.  Young people and women, who were very instrumental in bringing down Al Bashir were confident Sudan was on the right track.

Yet things have been complicated for over a year now. The Sudanese leadership was unpredictable. Sudan's stand on the Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD) was very confusing and unethical. At times Sudan was not defending its own interests and was not ready to compromise despite calls from concerned Sudanese intellectuals. It was  rather acting to satisfy the demands of Egypt, which was very unfortunate for Sudan. To make Sudan’s relationship with Ethiopia even worse and complicate things further, Sudan has been accused of supporting TPLF terrorist group that is waging war on Ethiopia, an important strategic neighbour of the Sudan. In short Sudan’s policy on Ethiopia was very confused depending on the civil or military leadership. Initially it sounded that Sudan’s civil government led by Prime Minister Abdalla Hamdok wanted to work with Ethiopia constructively, although it had challenges from the military, which has strong ties with Egypt.

The past one year therefore has been a challenge for Sudan’s Prime Minister, who was going through lots of pressure not only internally but also from western powers, especially the United Sates. USAID’s administrator Samantha Power was one of those putting undue pressure on Sudan and pushing it to the edge. For Administrator Power, it was all about getting what she wanted to achieve, not about Sudan’s strategic interest. It was about the Humanitarianism pretext and demanding changes at a pace Sudan was not able to cope with.

 

October 2021 was full of protests and unpredictability for Sudan. It is to be recalled Mr. Jeffrey Feltman, United States special Envoy for the Horn of Africa has been in the Sudan twice in a month time. Mr. Feltman who is not trusted by many in the Horn Of Africa had just departed the Sudan, when the military deposed the Civil government of Prime Minister Hamdok.  To make it even worse, the military has now declared state of Emergency and once again showed that it is not ready to hand over power to a civilian led government.  The hopes of those who sacrificed a lot in 2018 and 2019 and most recently are still on the air.

What does this change mean for Ethiopia?

The relationship between Ethiopia and Sudan has been very fragile for over a year now. Ethiopia and Sudan have yet to work on their boarder disputes, especially that of al-Fashaga. That would undoubtedly take time and patience to resolve. Ethiopia also wants Sudan to stop offering shelter to TPLF fighters, who fled to Sudan but have been training in the Sudan and trying to return to Ethiopia to join the TPLF terrorist group. Ethiopia is keen to see positive cooperation and a win-win situation on the stalled negotiation of the GERD. Ethiopia is keen to see a stable and prosperous Sudan that is ready to work with its neighbours constructively. That is why the Ethiopian Foreign Ministry Issued a statement following the coup in the Sudan.


In the meantime, Ethiopia has to be cautious and follow the situation in the Sudan very closely, whilst preparing itself for every eventuality. One thing is for sure, a strong and united Ethiopia is vital for the stability of the region as Ethiopia is an anchor country. That is what western powers ignore intentionally and support all those against Ethiopia.

Ethiopia could play vital roles as in the 2019 negotiation between the military and civil society if the need arises once again.

See how Prime Minister Abiy Ahmed was hailed for brokering the Sudan deal in 2019.


2 August 2021

ኢትዮጵያውያን ማንንም አንጠላም - ነገር ግን ሃገራችንን ሲነኩብን ዝም አንልም

 

እ.አ.አ ኖቬምበር 2020 መጀመሪያ ላይ ህውሃት በኢትዮጵያ የመከላከያ ጦር ላይ ያደረገውን ጥቃት ተከትሎ በትግራይ የተቀሰቀሰው ጦርነት ብዙ ዋጋ አስከፍሏል። በዚህ ጦርነት የብዙሃን ህይወት የጠፋ ከመሆኑም በላይ፤ በዙሃን ወገኖቻችን የአካል መጉድል፣ መፈናቀልና ልዩ ልዩ ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑ ይታወቃል። የጦርነት ምንም ደግ የለውም።

ይህን ጦርነት አሳዛኝ የሚያደርገው  በወንድማማቾችና እህትማማቾች መካከል የሚደረግ የተወሰኑ የስልጣን ጥመኞችን በዕብሪት የተሞላ ፍላጎት ለማሟላት በሚንቀሳቀስ አሸባሪ ኃይልና በተቃራኒው ደግሞ የኢትዮጵያን ህዝብና ሀገሪቷን የመጠበቅ ኃላፊነት ባለበትና በብዙሃኑ የኢትዮጵያ ህዝብ ድጋፍ ባለው የኢትዮጵያ ጦር ሰራዊት መካከል የሚደረግ ጦርነት መሆኑ ነው።

እንደሚታወቀው ህውሃት በኢትዮጵያ ለ27 ዓመታት በስልጣን በቆየበት ዘመን እጅግ በጣም አምባገነን ከመሆኑ የተነሳ እጅግ በጣም ብዙ ዘግናኝ የሆኑ ተግባራትን ሲፈፅም የቆየ ነው። ህወሃት በስልጣን ለመቆየት የኢትዮጵያን ህዝብ በዘር መከፋፈል ብቸኛው አማራጭ አድርጎ ስላመነ ህዝባችንን ለመከፋፈል የተቻለውን ሁሉ ሲያደርግ ቆይቷል። በብሄሮች መካከል ጥርጣሬ እንዲኖር፤ የጋራ አጀንዳ እንዳይኖርና ኢትዮጵያዊነት እንዲከስም ህወሃት ብዙ ሰርቷል።

ህወሃት ኖቬምበር 2020 ላይ የመከላከያ ኃይላችን ላይ ጥቃት ሲያደርግ የተለያዩ እሳቤዎችን ከገንዛቤ በመክተት እንደሆነ ይገመታል። በህወሃት ዕምነት የኢትዮጵያ ህዝብ ተከፋፍሏል። በህወሃት ዕምነት የኢትዮጵያን ሰራዊት በቀላሉ በማሸነፍ ስልጣን በቀላሉ መያዝ ይቻላል የሚል የተሳሳተና በዕብሪት የተሞላ ግንዛቤ ነበር። በህዋሃት ዕምነት በኢትዮጵያ የመንግስት ስልጣን መያዝ ብቻ ሳይሆን በኤርትራም የመንግስት ለውጥ ማምጣት ይቻላል የሚል እጅግ በጣም ሌሎችን አሳንሶ የማየት፤ እራስን ያለማወቅና የማግዘፍ ዝንባሌ ነበር።

በህዋሃትና ጥቂት ደጋፊዎቹ ውስጥ የተፈጠረው የበላይነት ስሜት የሌሎችን ጥንካሬ ለማየት እንዲሳናቸው አድርጓቸዋል። ለዚህም ሕወሃት ጦርነቱ እንደተጀመረ ይስጥ የነበረው መግለጫ ትልቅ ግንዛቤ ይሰጣል።

 

የህወሃቱ ሴኩቱሬ ጌታቸው ስለ ህወሃት አጥቂነትና ጠንካራነት ሲነግረን ህወሃት መብረቃዊ ጥቃት ማድረግ ብቸኛው አማራጭ እንደነበረ ነግሮናል። ይህ ትዕቢት የተሞላበት ንግግር ብዙዎችን አስቆጥቷል። ህወሃት በወቅቱ ጥቃት ሲፈፅም የነበረው ግንዛቤ መከላከያን ጨምሮ የተቀረው ህዝብ ምላሽ የማይሰጥና እራሱን መከላከል የማይችል አድርጎ አሳንሶ የማየት ዝንባሌ ነው። በሃገር ውስጥም ሆነ በውጭ ያለው የህወሃት ኃይልና ደጋፊ ትልቅ የሆነ የግንዛቤ ችግር ያለበት ባይሆን ይህ ጦርነት እዚህ ደረጃ አይደርስም ነበር። እነ አሉላ ሰለሞን ጦርነት ባህላዊ ጨዋታችን ነው ሲሉን፤ እነ ስየ አብርሃ ደግሞ ስለ ጦርነት እኛ ፊት እንዳታወሩ ይሉን ነበር። ይባስ ብሎ ፈረንጆቹ እነ ኸርማን ኮህንና ሌሎች አውሮፓውያን ህወሃትን ከሌላ ዓለም የመጣ ለማስመሰል ሞክረዋል።

ህወሃት ራሱን በራሱ ጠልፎ ከወደቀ በኋላ እንዴት ብቻዬን እውድቃለሁ በሚል ጦርነቱን ወደ ሌሎች ክልሎችና ሉዓላዊት ሀገር ወደ ሆነችው ኤርትራ ለመውሰድ ብዙ ጥሯል። ህወሃት አልተሳካለትም እንጂ የአፍሪካ ቀንድና ቀጠናውን ጦርነት ውስጥ ለመክተት ያላደረገው ጥረት የለም።

ህወሃት የኢትዮጵያን ህዝብ በዳይ ሆኖ ሳለ የምዕራብ ዓለም ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች፣ በኤክስፐርትነትና በስብዓዊ መብት ተቆርቋሪነት ስም ድብቅ ዓላማቸውን ከሚያከናውኑ ግለሰቦችና ተቋማት ከፍተኛ ድጋፍ ሲያገኝ ቆይቷል።

ምዕራባውያን ፖለቲከኞችና ሚዲያዎች ለህወሃት ድጋፍ ከመስጠት በተጨማሪ በኢትዮጵያ ላይ አላስፈላጊና መርህ አልባ የሆነ ተፅዕኖ ሲያደርጉ የቆዩ ሲሆን አንዳንዶቹ የአሜሪካና የአውሮፓ ባለስልጣናትና ቢሮክራት በኢትዮጵያ የመንግስት ለውጥ እንዲኖር እየሰሩ መሆናቸውን የሚያሳዩ ምልክቶች እየታዩ ነው። በዩጎዝላቪያ፣ ኢራቅ፣ ሊቢያ፣ ሶሪያና የመን እንዳደረጉት ሁሉ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ውስጥ ጣልቃ ለመግባት እየተዘጋጁ መሆናቸውን የሚያሳዩ ምልክቶች እየታዩ ነው።

የምዕራቡ ዓለም ፖለቲከኞች ጋ የግንዛቤ ችግር ያለ ይመስላል። ኢትዮጵያ የራሷ የሆኑ የቆዩና በመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ውስጥ ዘልቀው የገቡ የጋራ እሴቶች መኖራቸውን፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ለጠላት መቸም ቢሆን ተንበርክኮ የማያውቅ መሆኑን፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ከመቸውም በላይ በአንድነት ሆኖ ለሃገሩ ዘብ ለመቆም ዝግጁ መሆኑን፤ የኢትዮጵያ ጉዳይ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የመላው አፍሪካና የጥቁር ህዝቦች ጉዳይም ጭምር መሆኑን ግንዛቤ ውስጥ ያለማስገባት ሁኔታ ይታያል።

ኢትዮጵያውያን በፖለቲካ አመለካከት ልንለያይ እንችል ይሆናል። በተለያዪ ዓለማት ተበትነን እየኖርንም ሊሆን ይችላል። በሃገራችን ጉዳይ ግን በፍፁም አንደራድርም

ኢትዮጵያ ለሌሎች ሃገራት የምትሰጠውን ክብር ራሷም ማግኘት አለባት። ስለዚህ የአሜሪካና የአውሮፓ ፖለቲከኞችና ቢሮክራት በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ላይ የሚያደርጉትን ጣልቃገብነት መታገል ግዴታችን ነው ። ከማንም በፊት የኢትዮጵያን ጥቅም ማስጠበቅ የምንችለው እኛው ራሳችን ኢትዮጵያውያን ነን:: ኢትዮጵያውያን በፍፁም ችላ እንዳንል። 

ኢትዮጵያውያን ማንንም አንጠላም። ነገር ግን ሃገራችንን ሲነኩብን ዝም አንልም። በኢትዮጵያ ጉዳይ ዝምታ የለም። በፍፁም።

 

5 May 2021

EU is getting it wrong on Ethiopia- it is regrettable

I was a great fan of the European Union; great admirer of the system. I believed it was an institution that was for fairness, genuine human rights protection, democracy and rule of law. As a British citizen, I had chance to travel visa free across Europe; rights to work across Europe; European Health Insurance and many good things, I thought the union was good for Europe and a good model for other continents. 

When the United Kingdom went to the polls in June 2016 to decide on the EU referendum, I voted to REMAIN. UK decided to LEAVE. I have many good friends who voted LEAVE. When I asked them for their reasons for voting LEAVE, they often said, ‘EU is autocratic and doesn’t listen to citizens on the ground’. I can see that. 

All EU’s actions on Ethiopia since the November 2020 conflict are unfriendly, immoral and out of character. It looks it has lost a partner in the TPLF. It looks EU’s attitude for Ethiopia and for Africa is different from its attitude for Europe and other parts of the world. EU is trying to dictate a sovereign country. EU is trying to say, ‘do it my way or I will suspend this or that’. We recall that EU suspended developmental aid to Ethiopia following the conflict in Tigray. It wanted to interfere in the internal affairs of a sovereign state. When Ethiopia was bold and determined, EU changed its attitude. EU for sure knows Ethiopia is an important and strategic partner in Africa. That was why it once again made a statement on the strategic importance of Ethiopia for the European Union and started to work with Ethiopia. EU also decided to send observers to the June 2021 general election, which was a good sign of rebuilding relationships. EU even sent a team to observe the preparatory work. All these were welcomed by Ethiopia. 

Although Ethiopia welcomed EU’s decision to send observers to the June 5 general election, we have now learned that EU is not sending observers. The reasons are clear. Ethiopia is not bowing down to EU’s unconvincing demands. EU has put forward unusual conditions to Ethiopia to observe the June 5 election. According to the Ministry of Foreign Affairs of Ethiopia, EU has demanded that it should bring in telecommunication equipment for VSAT services if it were to observe the June general election. This has never happened; and why now? Ethiopia is ready and capable to provide telecom services during EU’s and indeed others’ stay in the country as observers. What makes EU so special to put this as a precondition to observe an election? To insist that EU should bring in equipment for VSAT services smells fishy; rather disrespectful and unexpected. Do they want to give the equipment to TPLF remnants and resuscitate TPLF from the ashes? 

EU shouldn’t forget that when it is in Ethiopia, it is only a guest, nothing more. 

Another demand by EU is very dangerous. EU has demanded that it wants to make public comments and announcement about the general election before even the National Board of Ethiopia. This is scandalous and seriously questionable. EU had observed Ethiopia’s sham elections in the past. It knew the elections were not democratic. Yet it didn’t have demands. So why now? 

Whether EU likes it or not, the June 5 general election will go ahead. Ethiopians don’t need validation by EU on their most important democratic exercise. Ethiopians decide, nobody else! Ethiopia will prevail and come out victorious in all fronts. One thing is for sure, EU also will come back; it is a matter of time. For the time being we say, thank you but not thank you! See you later, EU.

 

14 April 2021

GERD - Get it done no matter what!


As Ethiopia prepares for the filling of its most important dam, we have seen anger in some quarters in Egypt, which could be either intentional to create tension or total ignorance of the situation. Whatever the challenge, Ethiopia has to get its Dam done. 

If the origin of the Nile was Egypt, then Egypt might find a tap to stop the flow of Nile Waters. Fortunately that is not the case. To think as if the source of the Nile to be Egypt is disingenuous.  

No need to be angry at Ethiopia’s flagship project like 2 year old toddlers crying for everything they see. 

Egypt has to come to a negotiating table for a 21st century negotiation. Ethiopia is contributing 85% of the Nile Waters and deserves fair share. We all know Nile waters are more than enough for all. 

Vital to remember that both the 1929 & 1959 agreements are void and unacceptable as far as Ethiopia was concerned. Ethiopia is not a signatory to the party. 

Equally vital to stop intentionally ignoring the reality as it is for the benefit of all to come to a mutually acceptable agreement. It is not time for one side wins all and others remain bystanders. 

After all it is about Mutual Benefits, Reciprocity, and Sovereign Equality. This is 21st century, where we are interdependent on one-another and should cooperate; but that cooperation should be mutually sought based on mutual interests. 

4 April 2021

ከፊታችን የተደቀነውን ፈተና በጋራ ማለፍ ይገባል

የኢትዮጵያ ህዝብ በተለያየ ጊዜ ፈተናዎች አጋጥመውታል። ባለፉት 5 ወራት ግን ፈተናዎቹ ዘርፈ ብዙ ሆነዋል። ተደጋጋሚ ዘር ተኮር ጥቃቶች በትህነግ አነሳሽነት የተጀመረው ግጭትና ታላላቅ የሚባሉት እንደ ቢቢሲ እና ኤን ኤን ያሉ የሚዲያ ተቋማት የተዛባና እውነትን መሰረት ያላደረገ ዘገባ በሰብአዊ ድርጅት ስም የሚሰሩ እንደ አምነስቲና ሂውማን ራይትስ ዎች ያሉ ተቋማት ውስጥ ያሉ ድብቅ አላማ የተሸከሙ ግለሰቦችና ድርጅቶቹም ጭምር በግልፅ የሚታይ መርህ ያጣ ውንጀላ የአውሮፓ ህብረትና የአሜሪካ ቅጥ ያጣ ጉትጎታና ከልክ ያለፈ ጫና።


የኢትዮጵያ ጠላቶች ከዚህ የበለጠ ጫና ለመፍጠር ሊሞክሩ ይችላሉ። የሰው ኃይል የገንዘብና የቁሳቁስ አቅርቦት በማሟላት የበለጠ ጥፋት ለማስከተል 24 ሰዓታት ባለማቋረጥ ሊሰሩ ይችላሉ። ከምንም ጊዜ በላይ ጥንቃቄና አርቆ አስተዋይነት ያስፈልገናል:: ዛሬም እንደ ጥንቱ ተስፋ ያስፈልጋል። ከምንም በላይ አንድነት ያስፈልጋል።

እንደ ኢትዮጵያዊ ከመቼውም ጊዜ በላይ መደራጀትና ለአንድ አላማ መስራት ብቸኛው አማራጫችን ነው::

ከፊታችን የተደቀነው ፈተና መታለፉ አይቀርም። ፈተናዎቹ ቢበዙም ህዝባችን ዛሬም እንደ ጥንቱ በህብረት በመሆን ኢትዮጵያን ሊታደጋት ይገባል። ኢትዮጵያም ማሸነፏ አይቀርም።

በመላው ዓለም ያሉ ኢትዮጵያውያን ከመቼውም በላይ በህብረትና በብዛት በመሆን ስለ ኢትዮጵያ ሊጮሁና ለኢትዮጵያ ህብረት በትጋት ሊሰሩ ይገባል። ኢትዮጵያ ከመቼውም በላይ ልጆቿን ትሻለች::ሀገራችን ስትጠራን ደግሞ አቤት ማለት ምርጫችን ሳይሆን ግዴታችን ነው። ይህንን ግዴታችንን ጊዜ ሳንወስድ መወጣት አለብን። ሀገራችን የገባችበትን አጣብቂኝ ሁኔታም በሰከነ አዕምሮ መመርመር የግድ ይሏል።

በውጩ ዓለም የምንኖር ሰዎች ብዙ ጊዜ የምንገነዘበው ነገር አለ። በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የሚኖረው ፍጥጫ እጅግ በጣም ከባድ መሆኑን። ፓርቲዎቹ እስከ መጨራሻው የሚነጋገሩ አይመስሉም። የሀገር ጉዳይ ሲመጣ ግል ሁሉም በአንድነት ይቆማሉ። በፖለቲካ አመለካከት መለያየት፤ በሀገር ጉዳይ ግን አንድ መሆን በየትኛውም አለም ያለ ነው። ኢትዮጵያውያንም በሀገር ጉዳይ ላይ ቁርጥ የሆነ አቋም ሊኖረንና ለወደፊቱ ትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን ልናስረክበው ይገባል።

ኢትዮጵያዊነት ይለምልም።

25 February 2021

ሰገጤ ነኝ አለች ፤ እኔም ሰገጤ ነኝ

ሰገጤ ነኝ አለች

እኔም ተከተልኳት

እሷ ብቻ አይደለች

እኔም ሰገጤ ነኝ

ስለ ሀገር ማውራቷ

ከልብ መታከቷ

መጮህ መጨነቋ

ኢትዮጵያ ማለቷ

አንተን ካበሳጨህ

አንቺን ካናደደሽ

ችግሩ ካንተው ነው

ፈተናው ያንችው ነው

መድኃኒቱን እወቅ

መፍትሄ ፈልጊ

ሰገጤዎች ጎራ

ብዙ መፍትሄ አለ

ከመፍትሄው ዋናው

ወደርም የሌለው

የኢትዮጵያ ፍቅር

ፍቱን መድኃኒት ነው

 


The Global Refugee Forum – time for meaningful participation of Refugees

  As the Global Refugee Forum takes place between 13 - 15 December 2023 in Switzerland, it is vital that we have meaningful participation of...