1 March 2019

ሀገርን የምናድነው ጫፍና ጫፍ ሆነን እይደለም


በሀገራችን የተከሰተውን ለውጥ ተከትሎ የፖለቲካ ምህዳሩ እየሰፋ የመጣ ቢሆንም በተጓዳኝም ዘረኝነትና ፅንፈኝነት መስፋፋቱ የአደባባይ ሚስጥር ነው። የመናገርና የመፃፍ መብት ለእሱ/ለእሷ ብቻ የተፈቀደ የሚመስላቸው ቡድኖችን እያስተዋልን ነው። የእኔ ሃሳብ ብቻ ነው ትክክለኛ ሃሳብ የሚሉ ግለሰቦችና ቡድኖች በብዛት እያየን ነው። የዲሞክራሲ ባህል ባልዳበረበት ሀገር እያንዳንዱ እንቅስቃሴያችን ጥንቃቄ ያስፈልገዋል። የፖለቲካ ልሂቅ (Political elite)ነኝ የሚሉ ሰዎች በየአጋጣሚው የሚሰጧቸው መግለጫዎችና አስተያየቶች አርቆ አስተዋይነትን ማዕክል ያደረገ መሆን አለበት። ከብሽሽቅ ፖለቲካና ከፀብ አጫሪነት መጠንቀቅ ይገባል። ጊዜው የዲሞክራሲያዊ ባህል ግንባታ እንጂ የነጥብ ማስቆጠሪያ አይደለም

ለውጡን ተከትሎ ትናንት በአንድ ጎራ የነበሩት ዛሬ ሊለያዩ፤ በሌላ በኩል ደግሞ ትናንት ለየብቻ የነበሩ ዛሬ በጋራ ሲሰሩ ልናይ እንችላለን። በእርግጥ በፖለቲካው ዓለም ዘላለማዊ ወዳጅ ወይም ዘላለማዊ ጠላት የለም። የፖለቲካ ድርጅቶችም ሆኑ የተለየያ የፖለቲካ አመለካከት ያላቸው ግለሰቦች የጋራ አጀንዳቸውንና ፍላጎታቸውን ለማሳካት አመቺ ነው የሚሉትን አቅጣጫ ሊጠቀሙ ይችላሉ። ይህ አካሄድ ሊያስደነግጠን አይገባም።

ትልቁና አሳሳቢው ጉዳይ ፅንፈኝነት ነው። ጫፍና ጫፍ ሆኖ ማሸነፍ አይቻልም። መዘንጋት የሌለበት ጉዳይ አብዛኞው ህዝብ መሃል ላይ ያለ፤ ይበጀኛል የሚለውን ጠንቅቆ የሚያውቅና በጥሞና እየገመገመ ያለ መሆኑን ነው።  ህዝብ የማያውቅ ከመሰለን ትልቅ ስህተት ውስጥ ነው ያለነው። ህዝብ በጣም ያውቃል።

The Global Refugee Forum – time for meaningful participation of Refugees

  As the Global Refugee Forum takes place between 13 - 15 December 2023 in Switzerland, it is vital that we have meaningful participation of...