ኢትዮጵያዊነት ፍቅር ፤ ኢትዮጵያዊነት መቻቻል ፤ ኢትዮጵያዊነት መከባበር ፤ ኢትዮጵያዊነት
መንፈስ፤ ኢትዮጵያዊነት ፀጋ ፤ ኢትዮጵያዊነት የታላቅነት ምሳሌ ፤ ኢትዮጵያዊነት ብዙሃንነት ፤ ኢትዮጵያዊነት ህብረት ፤ ኢትዮጵያዊነት
የአኩሪ ታሪክ ባለቤትነትን ያካተተ ውስጡ ትልቅ ሚስጥር ያለው ነው፥፥ እነዚህንና ሌሎችን ኢትዮጵያዊ እሴቶች መሠረት በማድረግ በሀገራችን
ኢትዮጵያ የተጀመረውን የለውጥ ጉዞ ተግባራዊ በሆነ መልኩ ማገዝ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የሚጠበቅ ነው፥፥

ወደ ተግባራዊ እንቀስቃሴ ከመግባታችን በፊት የተወሰኑ ጥያቄዎችን ማየት ተገቢ ይሆናል
፥፥
1.
ሀገራችን ምን ያስፈልጋታል? ሀገራችን ምን አላት?
2.
ሌሎች ወገኖች
ምን እያደረጉ ነው?
3.
ለሀገራችን ከሚያስፈልገው ውስጥ የትኛውን በተሻለና በተደራጀ መልኩ ማገዝ እንችላለን?
4.
ይህንን ማከናወን የሚያስችል ስብስብ ውይም ግሩፕ አለን ወይ?
5.
እቅዳችንን ማገዝ የሚችሉ ተቋማትና ታዋቂ ግለሰቦች አሉ?
6.
ከነዚህ ተቋማትና ታዋቂ ግለሰቦች ጋር ትውውቀና ግንኙነት አለን?
7.
እቅዳችንን እንዴት ነው ተግባራዊ የምናደርገው?
8. እቅዳችንን ለህዘባችንና ለሚመለከታቸው ሁሉ እንዴት ነው የምናሳውቀው?
9.
የጊዜ ሰሌዳችን ምን ይመስላል?
ከላይ የተጠቀሱትንና መሰል ጥያቄዎችን በመመለስ የተደራጀ፣ ዘለቄታ ያለወና ብዙሃንን
ማሳተፍ የሚችል ተግባራዊ ስራዎቸን መስራት እንችላለን፥፥ ስለ ሀገር መነጋገርና በጋራ መስራት ለሁላችንም ይበጃል፥፥ በሀገራችን ጉዳይ ሁላችንም የሚያገባንን
ያህል ሀገራቸንን በተደራጀ መልኩ ማገዝ ብንችል ወጤቱ ሁላችንንም የሚያኮራና ከዘመን ዘመን የሚሸጋገር ሊሆን ይቸላል፥፥ ለመጪው
ትውልድም የተሻለ ነገር አስተምረን ማለፍ እንቸላለን፥፥ በተደራጀና ሁሉን ባሳተፈ መልኩ መስራት ከቻልን ሀገራችንን በሁሉ መልኩ
ልናግዛት እንችላለን፥፥ ይህንን ተግባራዊ የማድረጊያው ጊዜ ደግሞ አሁንና አሁን ብቻ ነው፥፥
ቸር እንሰንብት፥፥